Category: Latest News

በእንጅባራ ዩኒቪርሲቲ የእንሰሳት እርባታ ማዕከል የልምድ ልውውጥ ተካሄደ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የውጭ ዝርያ ያላቸውን የወተት ላሞች በመግዛት ማርባት የጀመረ ሲሆን በማዕከሉ የሚመረተውን ወተት በተመጣጣኝ ዋጋ በዋናነት ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እያቀረበ ይገኛል፡፡ማዕከሉ ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘዴን በመጠቀም የወተት ከብቶችን እያረባ እንደመሆኑ መጠን በአካባቢው በወተት ልማት ላይ ለተሰማሩ የእንስሳት አርቢዎች ተሞክሮውን የማካፈል ሥራ ተከናውኗል፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) […]

Read More

ለሀገር አቀፍ የግብርና ናሙና ቆጠራ ሰልጣኞች ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ

ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የግብርና ናሙና ቆጠራ ሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃግብር በእንጅባራ ዩኒቨርስቲ ተካሂዷል፡፡ በመርሐግብሩ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና ልማት ም/ፕሬዚደንት ወሀቤ ብርሃን(ዶ/ር) የግብርና መረጃዎችን ናሙና ለመሰብሰብ የሰለጠነ መረጃ ሰብሳቢ የሚያስፈልግ በመሆኑ ይህ የስልጠና ፕሮግራም መዘጋጀቱን ተናግረው በግብርና ናሙና አወሳሰድ ላይ ወቅታዊ፣ ተጨባጭና ተዓማኒነት ያለውን መረጃ ለማሰባሰብ የተዘጋጀውን […]

Read More

ከተለያዩ የጤና ተቋማት ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ተጀመረ

      ነሐሴ 15/2016 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከአማራ ብሄራዊ ክልል መንግስት ጤና ቢሮና ከአዊ ብሔረሰብ ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር ከተለያዩ የጤና ተቋማት ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች በተግባር የታገዘ የክትባት ስልጠና (Imunization in practice) መስጠት ጀምሯል። ስልጠናው ለተከታታይ 6 ቀናት የሚቀጥል መሆኑም ተገልጿል። የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን አቶ ዳንኤል አዳነ በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው […]

Read More

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የስንዴ ምርጥ ዘር መዝራት ተጀመረ

ዩኒቨርሲቲው የሚገኙ ከግንባታ ውጭ የሆኑ ቦታዎች ላይ የተለያዩ የሰብልና የአትክልት ዘሮችን በመዝራት ላይ ሲሆን በዛሬው እለት የስንዴ ምርጥ ዘር መዝራት ተጀምሯል፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት  ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ለማህበረሰብ አገልግሎት የሚውሉ የተሻሻሉ የሰብልና የአትክልት ዝርያዎችን ለማስፋፋት በምርምር የተደገፈ የምርጥ ዘር ብዜት እንደሚያከናውን ገልጸው በዛሬው እለት የተጀመረው በስድስት ሄክታር መሬት ላይ የሚዘራው  የስንዴ […]

Read More

የአንጎል እና ህብለ ሰረሰር ቀዶ ህክምና(Neuro Surgery) አገልግሎት ለመሰጠት ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል የአንጎል እና ህብለ ሰረሰር ቀዶ ህክምና (Neuro Surgery) አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት መደረጉን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል የማይሰጡ አግልግሎቶችን ከእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል አስተዳደር እና ከክልል ጤና ቢሮ ጋር በመቀናጀት ደረጃ በደረጃ የማስጀመር እና የእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታልን ደረጃ የማሻሻል ስራ እንደሚሰራ ጨምረው ተናግረዋል።በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና […]

Read More

ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ህክምና መጽሃፍት እና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገ

ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ህክምና መጽሃፍት እና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገ።ዩኒቨርሲቲው ከቅዱስ ፓውሎስ፣ ጥቁር አንበሳ እና የካቲት 12 ሆስፒታሎች ከ1 ሚሊዮን ብር ባለይ ግምት ያላቸው መጽሃፍት እና ቁሳቁሶች ድጋፍ ማግኘቱ ተገልጿል፡፡የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህር ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ቃለዓብ እሱባለው ድጋፉ የተገኘው ከቅዱስ ፓውሎስ፣ጥቁር አንበሳ እና የካቲት 12 ሆስፒታሎች መሆኑን ገልጸው 380 የሚሆኑ የህክምና መፅሃፍት ፣መድሃኒቶች እና […]

Read More

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ጋር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

የመግባቢያ ስምነነት ሰነዱ ሁለቱ ተቋማት በጋራ ለመሥራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑም ተገልጿል።የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ ቱሪዝም እና ሥራ ፈጠራ በሀገር ደረጃም ትኩረት የተስጠው ዘርፍ ከመሆኑም ባሻገር የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲም አንዱ የትኩረት መስክ መሆኑን በመጥቀስ በአካባቢው ያለውን እምቅ ያልተነካ የቱሪዝም ሀብት ለመጠቀም ልምድ ካለው ተቋም ጋር መስራት ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።ተቋማቱ […]

Read More

ለ “STEM” ተማሪዎች በተግባር የተደገፈ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ ሦስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ እና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በ2ኛ ዙር የክረምት መርሐ ግብር እየተማሩ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡ዩኒቨርሲቲው ከዚህ በፊት ከአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ በሳይንስ ትምህርቶች ላይ የተሻለ ውጤት ያላቸውን ተማሪዎች በክረምት እና በበጋ የሳምንቱ እረፍት ቀናት ሲያስተምር […]

Read More

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ተካሄደ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች እና የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሩ ላይ ተሳትፋዋል፡፡ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ እንደ ሀገር ትኩረት ለተሰጠው አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የራሱን ሚና እየተወጣ የሚገኝ ሲሆን በተለይም ባለፈው ዓመት ከአንድ መቶ ሺ በላይ ችግኝ መተከሉን የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ በዛሬው እለትም የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ እና የከተማው ወጣቶች በጋራ […]

Read More

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከአየሁ ጓጉሳ ወረዳ ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚሆን የቆርቆሮ ድጋፍ አደረገ

ዩኒቨርሲቲው በወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት ከአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር አየሁ ጓጉሳ ወረዳ ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ የሚሆን ከ1ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ከ1ሽህ 5መቶ በላይ ዚንጎ ቆርቆሮ ድጋፍ አድርጓል፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ለማህበረሰቡ በርካታ ድጋፎችን ሲያደርግ የቆየ መሆኑን ገልጸው በዛሬው ዕለት በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር አየሁ ጓጉሳ ወረዳ በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት […]

Read More