Author: Admin

በስርዓተ ትምህርት ዝግጅት እና ትምህርት ምዘና ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ

ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን በስርዓተ-ትምህርት ዝግጅት እና በትምህርት ምዘና ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሠጥቷል፡፡ ስልጠናውን የከፈተቱት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ እና ማጎልበቻ ኦዲቲንግ ስራ አስፈጻሚ ዓለም አምሳሉ( ዶ/ር) የስልጠናው ዓላማ መምህራን በትምህርት ምዘና እና በመማሪያ ግብዓቶች ዝግጅት ዙሪያ የተሻለ ግንዛቤን እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ስልጠናውን የሰጡት የዩኒቨርሲቲው የመምህራን ትምህርትና […]

Read More

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በአፕል ችግኝ ልማት ዙሪያ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በግብርና፣ ምግብና ዓየር ንብረት ኮሌጅ አማካኝነት ለዩኒቨርሲቲው አትክልተኞች በአፕል ልማት ዙሪያ የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በዩኒቨርሲቲው ሆርቲካልቸር መምህርና የስልጠናው አስተባባሪ የሆኑት አቶ አዲሱ ሙሉቀን በግቢው ውስጥ ከ3ሺ በላይ የደጋ አፕል ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰው ችግኞችን ለሚንከባከቡ አትክልተኞች ስለ አፕል አመራረት ዝርያና መረጣ፣ ቅጥያ ማስወገድን፣ መገረዝና በሽታ መከላከልን፣ ቀለበት የመስራትን ጠቀሜታ፣ […]

Read More

የማህፀን ጫፍ ቅድመ ካንሰር ምርመራ ዘመቻ ተጀመረ

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለሁለተኛ ዙር የተካሄደው የማህፀን ጫፍ ቅድመ ካንሰር የግንዛቤ ፈጠራ እና የምርመራ ዘመቻ ተጀምሯል፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል(CPD)አስተባባሪ ወ/ሮ የውብምርት ሻረው(ረዳት ፕሮፊሰር) ከነሐሴ 21/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለተኛ ዙር የማህፀን ጫፍ ቅድመ ካንሰር የግንዛቤ ፈጠራ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ጋር በመተባበር የምርመራ ዘመቻ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡ አክለውም […]

Read More

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በዚገም ወረዳ ለሚገኙ ተፈናቃዬች የምግብ ድጋፍ አደረገ

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በአዊ ብሄረሰብ አስተዳዳር ዚገም ወረዳ በጸጥታ ችግር ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች 121 ኩንታል በቆሎ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ የፎረሙ ዋና ጸሐፊ ታፈረ መላኩ(ዶ/ር) በአማራ ክልል ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች የተቋቋመው ፎረም የማህበረሰቡን ችግር ከመፍታት አንጻር የጋራ ጥናትና ምርምር ከማድረግ ባሻገር በክልሉ በተለያዩ ጊዜያት በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ምክንያት ለሚከሰቱ ችግሮች ምላሽ በመስጠት የተለያዩ […]

Read More

በእንጅባራ ዩኒቪርሲቲ የእንሰሳት እርባታ ማዕከል የልምድ ልውውጥ ተካሄደ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የውጭ ዝርያ ያላቸውን የወተት ላሞች በመግዛት ማርባት የጀመረ ሲሆን በማዕከሉ የሚመረተውን ወተት በተመጣጣኝ ዋጋ በዋናነት ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እያቀረበ ይገኛል፡፡ማዕከሉ ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘዴን በመጠቀም የወተት ከብቶችን እያረባ እንደመሆኑ መጠን በአካባቢው በወተት ልማት ላይ ለተሰማሩ የእንስሳት አርቢዎች ተሞክሮውን የማካፈል ሥራ ተከናውኗል፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) […]

Read More

ለሀገር አቀፍ የግብርና ናሙና ቆጠራ ሰልጣኞች ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ

ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የግብርና ናሙና ቆጠራ ሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃግብር በእንጅባራ ዩኒቨርስቲ ተካሂዷል፡፡ በመርሐግብሩ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና ልማት ም/ፕሬዚደንት ወሀቤ ብርሃን(ዶ/ር) የግብርና መረጃዎችን ናሙና ለመሰብሰብ የሰለጠነ መረጃ ሰብሳቢ የሚያስፈልግ በመሆኑ ይህ የስልጠና ፕሮግራም መዘጋጀቱን ተናግረው በግብርና ናሙና አወሳሰድ ላይ ወቅታዊ፣ ተጨባጭና ተዓማኒነት ያለውን መረጃ ለማሰባሰብ የተዘጋጀውን […]

Read More

ከተለያዩ የጤና ተቋማት ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ተጀመረ

      ነሐሴ 15/2016 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከአማራ ብሄራዊ ክልል መንግስት ጤና ቢሮና ከአዊ ብሔረሰብ ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር ከተለያዩ የጤና ተቋማት ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች በተግባር የታገዘ የክትባት ስልጠና (Imunization in practice) መስጠት ጀምሯል። ስልጠናው ለተከታታይ 6 ቀናት የሚቀጥል መሆኑም ተገልጿል። የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን አቶ ዳንኤል አዳነ በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው […]

Read More

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የስንዴ ምርጥ ዘር መዝራት ተጀመረ

ዩኒቨርሲቲው የሚገኙ ከግንባታ ውጭ የሆኑ ቦታዎች ላይ የተለያዩ የሰብልና የአትክልት ዘሮችን በመዝራት ላይ ሲሆን በዛሬው እለት የስንዴ ምርጥ ዘር መዝራት ተጀምሯል፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት  ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ለማህበረሰብ አገልግሎት የሚውሉ የተሻሻሉ የሰብልና የአትክልት ዝርያዎችን ለማስፋፋት በምርምር የተደገፈ የምርጥ ዘር ብዜት እንደሚያከናውን ገልጸው በዛሬው እለት የተጀመረው በስድስት ሄክታር መሬት ላይ የሚዘራው  የስንዴ […]

Read More

የአንጎል እና ህብለ ሰረሰር ቀዶ ህክምና(Neuro Surgery) አገልግሎት ለመሰጠት ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል የአንጎል እና ህብለ ሰረሰር ቀዶ ህክምና (Neuro Surgery) አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት መደረጉን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል የማይሰጡ አግልግሎቶችን ከእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል አስተዳደር እና ከክልል ጤና ቢሮ ጋር በመቀናጀት ደረጃ በደረጃ የማስጀመር እና የእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታልን ደረጃ የማሻሻል ስራ እንደሚሰራ ጨምረው ተናግረዋል።በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና […]

Read More

ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ህክምና መጽሃፍት እና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገ

ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ህክምና መጽሃፍት እና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገ።ዩኒቨርሲቲው ከቅዱስ ፓውሎስ፣ ጥቁር አንበሳ እና የካቲት 12 ሆስፒታሎች ከ1 ሚሊዮን ብር ባለይ ግምት ያላቸው መጽሃፍት እና ቁሳቁሶች ድጋፍ ማግኘቱ ተገልጿል፡፡የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህር ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ቃለዓብ እሱባለው ድጋፉ የተገኘው ከቅዱስ ፓውሎስ፣ጥቁር አንበሳ እና የካቲት 12 ሆስፒታሎች መሆኑን ገልጸው 380 የሚሆኑ የህክምና መፅሃፍት ፣መድሃኒቶች እና […]

Read More